Tuesday, September 29, 2015

ጤና ይስጥልኝ ይህ የኢትዮ ኖርዌይ ቲቪ ሳምንታዊ የዜና ዘገባ ነው

ኢትዮጵያ ያሰረችውን የአለም ባንክ አስተርጓሚ እንድተፈታ ተጠየቀች
ታሳሪው ፓስተር በሽብርተኘነት ተከሰዋል
ግብጽ ጦሯን እያደራጀች ነው ከአፍሪካ ቀዳሚ የሚያደርጋትን የጦር መርከቦች ለመግዛትም ተቃርባለች
የኢትዮጵያ የጸረ ሙስና ኮሚሽነር ልማቱ እንዳይደናቀፍ በመስጋት ትልልቅ ሙሰኞችን እንደማይከሱ ተናገሩ
---

Wednesday, September 23, 2015

ጤና ይስጥልኝ ይህ የኢትዮ ኖርዌይ ቲቪ ሳምንታዊ የዜና ዘገባ ነው

የአውሮፓ ህብረት ዲፕሎማቶች የኢትዮጵያ ግድብ በአካባቢው በሚገኙ ማህበረሰቦች ላይ አደገኛ        ተጽእኖ እንደሚያሳድር ገለጡ
  • ዛሬም ኢትዮጵያዊያን ህይወታቸውን ለሞት እያጋለጡ ይሰደዳሉ
  • የኖቤል የቀድሞ ዳይሬከተር ለኦባማ የሰላም ሽልማት በመሰጠቱ እንደሚጸጸቱ ይፋ ይፋ አድርገዋል




Wednesday, September 16, 2015

እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ለህዳር 21 ተቀጠሩ – ‹‹የሽብር ተከሳሽ በመሆናችን ህክምና ተከልክለናል›› ተከሳሾቹ


Ethiopian youth commitment to freedom
የኢትዮ-ኤርትራ ድንበርን አቋርጠው ኤርትራ የሚገኘውን ግንቦት ሰባት የተባለ በተወካዮች ም/ቤት ሽብርተኛ የተባለ ድርጅትን ሊቀላቀሉ ሲሄዱ ተይዘዋል በሚል የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ በድጋሜ ለብይን ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

የዝች ምስኪን ደም ይጮሃል!

ኄኖክ ኄኖክ's photo.
ወጣት ሰሎሜ ጉልላት በሞራልም ሆነ በግብር ከወደቁና የስርኣቱን ዙፋን ለማስጠበቅ ተመልምለው መሳርያ ከታጠቁ የፌዴራል ፖሊስ አባላት በአንዱ በተከታታይ የጥይት ድብደባ ህይወቷ አልፏል። በነኝህ ሃይሎች ንፁሃን ዜጎቻችን (በተለይም ሴት እህቶቻችን) እንዲህ ላለው አደጋ ሲጋለጡ ይህ የመጀመርያ አይደለም። "የሴቶችን መብት አስከበርሁ" እያለ በሰርክ ፈሊጡ ፕሮፓጋንዳውን የሚነፋብን ይሄው ስርኣትም ሴቶች ላይ "ነፃ እርምጃ" በሚመስል አኩዋሃን ውድ ህይወታቸውን ያለስስት በአረመኔዎች እያስቀጠፈ ይገኛል። በታጠቁት መሳርያ የግል ቂማቸውን መወጫ ያደረጉ ጠባቂዎቹንም እንደተለመደው ሁሉ "እኛን አይወክሉም" በሚል ጥቅስ ሸፋፍኖ እንደሚያልፈውም የሚጠበቅ ነው። እኛ ግን እንላለን፦ ከሰማይም ይሁን ከምድር ፍትህ ለሰሎሜ!
ነፍስሽን በገነት ያኑር

አምሮቴ

ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ 
ምድር ስታጌጥ አድማስ ሲፈካ
ከሚገዳደር ያንቺን ሕላዌ
ዘገር ከሚሰብቅ ከክፉ ደዌ
ከዘውጌ ልምሻ ሥርየት አግኝተሽ 
የፍትሕ ጸበል ቡራኬ ጠጥተሽ
በሕዝብሽ ኅብር ተውበሽ ፈክተሽ
በዓለት ላይ ቁሞ ያንድነት ካስማ
እናፍቃለሁ ደግ ነገር ላይ፣በጎ ልሰማ
ከፍ ብለሽ ላይሽ በክብር ማማ፤ 
የፈጠረቀሽ-ክፉ ፃረ ሞት-ራሱ ታንቆ
ሕያው እስትንፋስ ከከርስሽ ፈልቆ
ሥርየት ስታገኝ ህልም አልማለሁ 
ጧቱ እንዲያምርልሽ ሰርክ እመኛለሁ፡፡ 
መጣሁ ሲል ዘመን-ልቤ ይጎናል-ተስፋ ያንቀኛል
ትንሣኤ አግኝተሽ-ክፉ ቀን አልፎ-ማየት ያምረኛል፡፡
ዘር ሳይዘራ-ሙቶ እንዲነሣ-ሳይኮተኮት ውኃ ሳይጠጣ
ከጥላቻ ሥር-ከጠብ አዝመራ-ማየት ያምረኛል መሲህ ሲወጣ
የሚያስከብርሽ-ውርደት ዝቅታን-አሻፈረኝ ባይ

Tuesday, September 15, 2015

የዝች ምስኪን ደም ይጮሃል!

ኄኖክ ኄኖክ's photo.
ወጣት ሰሎሜ ጉልላት በሞራልም ሆነ በግብር ከወደቁና የስርኣቱን ዙፋን ለማስጠበቅ ተመልምለው መሳርያ ከታጠቁ የፌዴራል ፖሊስ አባላት በአንዱ በተከታታይ የጥይት ድብደባ ህይወቷ አልፏል። በነኝህ ሃይሎች ንፁሃን ዜጎቻችን (በተለይም ሴት እህቶቻችን) እንዲህ ላለው አደጋ ሲጋለጡ ይህ የመጀመርያ አይደለም። "የሴቶችን መብት አስከበርሁ" እያለ በሰርክ ፈሊጡ ፕሮፓጋንዳውን የሚነፋብን ይሄው ስርኣትም ሴቶች ላይ "ነፃ እርምጃ" በሚመስል አኩዋሃን ውድ ህይወታቸውን ያለስስት በአረመኔዎች እያስቀጠፈ ይገኛል። በታጠቁት መሳርያ የግል ቂማቸውን መወጫ ያደረጉ ጠባቂዎቹንም እንደተለመደው ሁሉ "እኛን አይወክሉም" በሚል ጥቅስ ሸፋፍኖ እንደሚያልፈውም የሚጠበቅ ነው። እኛ ግን እንላለን፦ ከሰማይም ይሁን ከምድር ፍትህ ለሰሎሜ!
ነፍስሽን በገነት ያኑር

Monday, September 14, 2015

ጤና ይስጥልኝ እንኩዋን ለአዲሱ አመት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ


አዲሱ አመት 2008 የሰላም የፍቅር የጤና እንዲሆንልን እየተመኘሁ ከኢትዮ ኖርዌይ ቲቪ የሚተላለፈውን ሳምንታዊ የዜና ዘገባ በይት የዘገባ ዕርዕሶችን  በማስቀደም ዜናውን የማሰማችሁ ርሴማ መድህኑ ንኝ 

Monday, September 7, 2015

አትሌቱ እስካሁን የት እንዳለ አይታወቅም

 የዓረና ትግራይ ደጋፊ ነበር ወያኔ ዓረናዎችን በጣም ነው የሚፈራቸው በማራቶን ሩጫ አገራችንን ካስጠሩት ወጣት አትሌቶች አንዱ አብርሃ አማረ በቅርቡ ለውድድር ወደ ካናዳ ከተጓዘ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ መመለሱና አለመመለሱ አልታወቀም። በአዲስ አበባ ያለው የልሳነ ህዝብ ዘገጋቢ እንደገለፀው አብርሃ የዓረና ትግራይ ደጋፊ እንደነበርና በዚሁ ምክንያትም በአዲስ አበባ ከተማ የሰራው የግል ቤቱ በመንግስት ሰዎች ካለምንም የፍርድ ቤት ትእዛዝ በፖለቲካ ውሳኔ ብቻ ተቀምቶ ለአንድ የወያኔ ኢህአዴግ ባለስልጣን ስንደተሰጠ ለማረራገጥ ችሏል። አብርሃ በዚሁ ፖለቲካ ተሳትፎወ ምክንያት በፖሊሰ ቁጥጥር ስር ውሎ እንደነበረና ከእስር ቤት ከወጣ በሁዋላ ደስተኛ እንዳልነበር ከቅርብ ምንጮቻችን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። አብርሃ ሙሉ እራሱ የትግራይ ተወላጅ በመሆኑ ምክንያት ዓረና ትግራይን መደገፉ ከማንኛውም ተቃዋሚ በላይ ወያኔዎችን እንደሚያናድዳቸው ይታወቃል። አትሌት አብርሃ ሙሉ በበርካታ ኢንተርናሽናል ውድድሮች የአገራችንን ባንዲራ አንግቦ ለክብራችን የሮጠ ኢትዮጵያዊ ሲሆን በ2008 በቫሌንሺያ ፣ በ2009 ፖላንድ ዋርሶውና በሳን አንቶንዮ አሜሪካ፣ 2011 በግራን ካናሪያ ስፔንና በ2011 ሉብጂ ሉብጃና 1ኛ በመውጣት በሁለቱም አገሮች የወርቅ ሜዳሊያ ተሸልሟል። በ2014 በቻይና ተወዳድሯል። በመጨረሻ በ2015 በቶሮንቶ ካናዳ ከወዳደረና ውድድሩን በ2ኛነት ከካጠናቀቀ በሁዋላ ወዴት እንደገባ ሳይታወቅ ቀርቷል። አንዳንድ ሰዎች አትሌቱ ከመንግስት ጋር ከነበረው ግጭት በመነሳት ምናልባት ወደዳገር ቤት ተመልሶ በወያኔ ደህንነቶች ታፍኖ ሊሆን ይችላል ሲሉ አንዳንዱ ደግሞ ምናልባት ወዳገር ቤት ሳይመለስ ቀርቶ ይሆናል ይላሉ። ወያኔ እንደ የዓረና ትግራይ ደጋፊና አባላት የሚያስፈሩት ያህል ምንም ነገር አያስፈራውም፡፡ ወያኔ ሙሉ በሙሉ ይደግፈኛል እያለ የሚመካበት የትግራይ ህዝብ እንደካደው ሲያውቅ በተጠርጣሪ የትግራይ ሰዎች ለይ የሚያደርሰው ቅጣት ከባድ ነው። ምናልባት አትሌት አብርሃ ሙሉንም መቀጣጫ ለማድረግ ሲል አፍኖት ሊሆን ይችላል። ስለ አትሌቱ ዕውቀት ያላችሁ ታዳሚዎቻችን lisanehizb@mail.com ላይ ኢሜይል እንድትልኩልን በትህትና እንጠይቃለን። አትሌታችን ሰላም እንዲሆንም እንመኝለታለን።  

ጤና ይስጥልኝ ይህ የኢትዮ ኖርዌይ ቲቪ ሳምንታዊ የዜና ዘገባ ነው ዜናውን የማሰማችሁ ኣርሴማ መድህኑ ንኝ በመጀመርያም ኣበይት የዘገባ ዕርዕሶችን


በእስር ላይ የሚገኙ ሦስት እንስት ኢትዮጵያዊያን  በዓለም ላይ ከተመረጡ 20 የፖለቲካ እስረኞች መካከል ተካተቱ
ሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪዎች የአንድ ወር ዘመቻ ያደርጉላቸዋል
ግንቦት ሰባትን ለመቀላቀል ሲሄዱ ተያዙ በተባሉት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ላይ የፓርቲው አባል መሰከረ
ኦባማ በኢትዮጵያ ቆይታቸው 1.3ሚልዮን ዶላር ወጪ ማድረጋቸው ተነገረ