Friday, November 27, 2015

ወደ እስር ቤት ተወርውሮ የተረሳው ኦኬሎ አኳይ ኦቻላ


አንድ የኖርዌይ ዜጋ በውጭ አገር እሰር ቤት ተጥሎ የሞት ፍርድ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል። ለበርካታ ዓመታት እስርቤት ህወቱን እንደሚገፋ መገመት አያዳግትም። የኖርዌጂያን ጆሮ ዳባልበስ ማለት ኦኬሎ አኳይ ኦቻላን በከሳሾቹ ፊት ብቻውን እንዲቆም አድርገነዋል ሲሉ በኖርዌ የጸረ ዘረኝነት ማዕከል ሓላፊ የሆኑት ጠበቃ ሩነ ቤርገሉንድ ስቲን እና ምክታላቸው ኤቪን ኮህን ዳግስ ብላ ለተባለው የኖርዌይ ጋዜጣ አሳወቁ። በ 2009 ቶስቶቨ ሙላንድ እና ዩሽዋ ፍሬንች  በተሳሩበት ወቅት በተከታታይ ይዘግቡ ነበር:: የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም በተከታታይ ለህዝብ ያሳውቅ ነበር። ታዲያ የኦኬሎ አኳይ ኦቻላስ ጉዳይ ለምን  ችላ ተባላ?። ኦኬሎ የኖርዌይ ዜጋ ነው ወደ ኖርዌይ የመጣው በስደት ነው ላለፉት ሁለት ዓመታት በ ኢትዮጵያ በ እስር እየማቀቀ ነው የፍርዱ ሂደት በቅርብ ይጀመራል:: በዚች ምድር ሊረዳው የሚችል ቢኖር እኛው ነን ታዲያ ለምን አንረዳውም? ሚዲያዎች ለምን ጸጥ ረጭ ማለትን መረጡ ሲሉ ይሞግታሉ።
ጉዳዩ በጣም አሳሳቢ ከፍተኛ ጉዳይ ነው። ኦኬሎ የጋምቤላ ፕሬዚዳንት በነበረበት ወቅት በ 2003 400  የአኝዋክ ብሔረሰቦች በጥይትና በመጥረቢያ ሲጨፈጨፉ በመቃወሙና ራሱም አደጋ ውስጥ በመውደቁ ነው ለስደት የበቃው። ኦኬሎ ራሱ የአኝዋክ ቤሔረሰብ አባል ነው። በተባበሩት መንግስታት እውቅና ያገኘና በኖርዌይ ዜግነት ያለው ስደተኛ ነው። አራቱ ልጆቹና ባለቤቱ ኖርዌይ ውስጥ ይኖራሉ። እንደ ኦኬሎ እነሱም የኖርዌይ ዜጋ  ናቸው። አሁን ባለቤቱም የትዳር አጋሯን ልጆቹም አባታችውን ትተዋት ከተሰደዱባት አገር ኢትዮጵያ ውስጥ እስርቤት እየማቀቀ መሁኑን እያወቁ ምንም ማድረግ ስለማይችሉ ቁጭ ብለዋል፡:
የኢትዮጵያ መንግስት ኦኬሎ ገንዘብ ሰብስቦ ተዋጊ ቡድን ሲመለምል ይዘነዋል በሚል በሽብርተኝነት ክስ ከሶታል። የሺብርተኝነት ክስ የኢትዮጵያ መንግስት ተቃዋሚዎችን ለመምታት በብዛት ይጠቀምበታል። የኦኬሎ ጉዳይም ቢሆን የፈጠራ ክስ ላለመሆኑ ምንም መረጃ የለም። ኢትዮጵያ ውስጥ ዲሞክራሲ የሚባል ነገር አይታወቅም ታይቶም አያውቅም ሲል ዳግስ ብላ የተባለው የኖርዌይ ጋዜጣ ዘግቡአል። ከበርካታ የጦርነት አመታት በሁአላ ኢትጵያ የሰባዊ መብት በሰፊው የሚጣስባት የራሷን ህዝብ የምታሰቃይ በብዛት ጋዜጠኞች የታሰሩባትና የሕግ ሰርዓቱ ለገዥው መንግስት ከለላ የሆነባት አገር ናት ብሏል።

የኖርዌይ ባለስልጣኖች ኦኬሎን ለመጎብኝት ተከልክለዋል:: ይህ ደግሞ በኣገሮች መካከል ሊኖር የሚገባውን የዲፕሎማሲ ስምምነት ህግ የጣሰ ነው። በስቶኮልም የሚገኘው  የኢትዮጵያ ኢምባሲ ጉዳዩ ግልጽ ያለመሁን ነገር ነው ሲል ጉዳዩን አለባብሶታል። ኖርዌይ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ እርዳታ ከሚለግሱ አገሮች አንዷ ናት። ምንም  እንኳን እርዳታን ከአንድ ግለሰብ አያያዝ ጋር በቀጥታ ማገናኘት ራሱን የቻለ ችግር ቢኖረውም የኖርዌይ ባለስልጣኖች ጉዳዩን ከዚህ የበለጠ አጠንከረው ሊሄዱበት ይገባ ነበር፡፤ ኦኬሎ እንደ ኖርዌጂያን ዜጋ ከኖርዌይ ውጭ ሃላፊነት ወስዶ ሊያግዘው የሚችል አገር አይኖርም። እኛ ካረዳነው ማስቀያት ወይም ቶርቸር የቀን ከቀን ስራ በሆነባት አገር ኢትዮጵያ ውስጥ ለረጅም አመታት መታሰርን መጠባበቅ ግዴታ ይሆንበታል።
ሁማን ራይትስ ዎችና አመነስቲ ስለ ኦኬሎ ጉዳይ ደወላቸውን እያቃጨሉ ነው። ይሁን እንጂ ሚድያዎች ትኩረት ሊሰጡት ኣልቻሉም ዳግስ ባላ ከተባለው የኖርዌይ ጋዜጣ በስተቀር።  የኖርዌይ ማህበረሰብ ዝምታ ለኦኬሎ ከፍተኛ ጉዳት አለው። የኢትዮጵያ መንግስት በእርዳታ ላይ የቆመ መንግስት ስለሆነ ያልሆነው ዲሞክራት ሰብ አዊመብት ጠባቂ መስሎ መታየት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ዝምታው ይመቸዋል ማለት ነው። የሁሉቱም አገሮች ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ከህዝቡና ከሚዲያዎች ከፍተኛ ጫና ያስፈልጋል። ይህ ሳይሆን ቢቀርና በ ኦኬሎ ላይ ፈረደ ገምድል አይነት ፍርድ ቢፈረድበት ያስተዛዝበናል በኖርጂያን ዜጎች መካከል ልዩነት አለ እንዴ? ያሰኛል ሲሉ የኖርዌይ የጸረ ዘረኝነት ማዕከል ሓላፊዎች ለዳግ ብላ ሪፖርት አድርገዋል። ሪፖርቱ ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ ከ 100 ሺ በላይ በሆኑ ሰዎች ተደግፏል ወይመ ላይክ ተደረጓል፡፡

No comments:

Post a Comment