Saturday, May 28, 2016

ግንቦት ፳ እና ፈንጠዝያዉ አርሴማ መድህኑ ኖርዌይ ግንቦት 19/2008

 በደም የተገነባ፣ በደም የተለወሰ፣ በደም የሚያበራ፣ በደም የሚታደስ፣ ደም ግብሩ የሆነ ቀን ሲከበር የሚከፋችሁ ለምንድን ነው? ደም፣ ደም፣ ደም..... "ያለምንም ደም፣ ኢትዮጰያ ትቅደም" ተብሎ ተጀምሮ በደም ተቋጨ። "ካሁን በኋላ ጠላታችን ድህነት ብቻ ነው፣ ሰላማችንን የሚነካው የለም" በሚል ስብከት ተጀምሮ ይኽው አሁን ድረስ ደም እየተገበረ ነው። አሁን ባለው አያያዝ የግንቦት 20 ወዳጆች ደም የሚጠግቡ አይመስልም፣ገና ብዙ ደም ለማፍሰስ የተዘጋጁ ይመስላል። ክብር ለተስፈነጠሩት ባለ "ራዕዩ" መሪ!! በዚህ ቀን ዋዜማ ይህንን ጽሁፍ ሳዘጋጅ "የጫካውን ዘመን ሳናስብ 25 ዓመት ለመማር አይበቃም? "ብዬ ራሴን ጠይቄ ነበር። ተማር ያለው ከሌሎች ሲማር፣ የግንቦት 20 ባለቤቶች ለምን ለመማር ፈቃደኛ አይሆኑም? ከቶውንም ሊገባኝ የማይችል

Sunday, April 17, 2016

Ethiopia says South Sudanese gunmen kill 140 civilians


Minister says troops may cross border to pursue assailants after deadly raid in Ethiopia's Gambela region.

Gunmen from South Sudan have killed at least 140 civilians, including women and children, in a raid in Ethiopia's Gambela region, according to the Ethiopian government.

Getachew Reda, Ethiopia's communications minister, said on Saturday that Friday's attack had been carried out by members of South Sudan's Murle tribe.

He added that Ethiopian forces have killed 60 of the assailants and may cross into neighbouring South Sudan to pursue them.
"They haven't crossed the border [yet], but they will if that's what it takes," he told Al Jazeera.
The minister, who said the latest attack is much larger than past skirmishes, also said that a number of children have been abducted from Ethiopia and taken into South Sudan, according to an Associated Press news agency report.
The attackers had no relation to South Sudan's army or rebel forces who fought the government in Juba [Al Jazeera]
The attack happened in Gambela's Jakawa area which straddles the Ethiopian-South Sudanese border, in a region that alongside a neighbouring province hosts more than 284,000 refugees from South Sudan who fled conflict in the world's youngest nation.
The attackers had no relation to South Sudan's army or rebel forces who fought the government in Juba in a civil war that has killed tens of thousands of people, a statement from the government communications office said.
David Shinn, a professor of International Relations at George Washington University and former US ambassador to Ethiopia, said the region has a long history of ethnic conflict originating on both sides of the Ethiopia-South Sudan border.
"The border is porous and movement back and forth between South Sudan and Ethiopia is common," he told Al Jazeera.
"The conflict in South Sudan has resulted in refugees moving into Ethiopia. Rebel groups can also move across Gambela region. It is not surprising there are occasional local outbreaks of violence in this area."
South Sudanese officials were not immediately available for comment.
With reporting by Teo Kermeliotis: @Teo_Kermeliotis
Source: Al Jazeera and agencies

Thursday, April 14, 2016

አይ ኤም ኤፍ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ቁልቁል መምዘግዘጉን አስታወቀ

(ሳተናው) አለም አቀፉ የሞኒታሪ ፈንድ የአገራትን ዓመታዊ የኢኮኖሚ እድገት በማስመለከት ባወጣው ሪፖርት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ቁልቁል መምዘግዘጉን አስታውቋል፡፡

ምስራቅ አፍሪካዊቷ አገር በ30 ዓመታት የቅርብ ግዜ ታሪኳ ውስጥ አስተናግዳው የማታውቀውን አይነት ከፍተኛ ድርቅ በማስተናገዷ 100 ሚልዮን ከሚገመተው ህዝቧ አምስት ከመቶ የሚሆነው የምግብ እርዳታ የሚፈልግ ሆኗል ያለው አይ ኤም ኤፍ ለዚህም 1.4 ቢልዮን ዶላር መጠየቁን አስታውሷል፡፡
ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያ ፈጣን የተባለ የኢኮኖሚ እድገት(10.2%)ማስመዝገቧን የገለጸው ተቋሙ በዚህ ዓመት ኢኮኖሚው ወደ 4.5% ማሽቆልቆሉን በአግራሞት አስፍሯል፡፡የኢኮኖሚው እድገት በአገሪቱ የተፈጠረውን ድርቅ ተከትሎ በዚህ አመት 8.1% እንደሚሆን ተገምቶ ነበር ያለው አይ ኤም ኤፍ በ2017 የኢኮኖሚ እድገቱ 7 ከመቶ ይሆናል ተብሎም ተተንብዮ ነበር ብሏል፡፡
አይ ኤም ኤፍ በሪፖርቱ ከአፍሪካ አገራት መካከል አይቮሪ ኮስት፣ኬንያ፣ሩዋንዳና ሴኔጋል ከ6-7 ከመቶ የኢኮኖሚ እድገት በያዝነውና በቀጣዩ ዓመት እንደሚያስመዘግቡ ትንበያውን አስቀምጦላቸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ከወር በፊት የመንግስታቸውን የስድስት ወራት ሪፖርት ለፓርላማው ባቀረቡበት ወቅት ላለፉት አስርት አመታት እንደ ዶግማ ተይዞ የነበረው የሁለት ዲጂት የኢኮኖሚ እድገት ገለጻ በዚህ አመት እንደማይኖር በማውሳት የኢኮኖሚ እድገቱ በአንድ ዲጂት እንደሚሆን መናገራቸው አይዘነጋም፡፡
በአንጻሩ የጠቅላይ ሚንስትሩ የኢኮኖሚ አማካሪ የሆኑት ዶክተር አርከበ ዕቁባይ የኢኮኖሚ እድገቱ ዘንድሮም ሁለት ዲጂት እንደሚያስቆጥር መግለጻቸው ይታወሳል፡፡
ምንጭ ሜይል ኤንድ ጋርዲያን አፍሪ

የኢህኣዴግ ውጥረትና የኣቦይ ስብሓት ጭንቅ

ሰሞኑን ኢህኣዴግ በኣዲስ ኣበባ ስብሰባ ማካሄድ ጀምሮ ነበር።

ስብሰባው ከተጠበቀው በላይ ውጥረት የተሞላበትና የድርጅቶች ሞቧደን የታየበት ነበር። ቡዱኖቹ ህወሓትና ደህዴን በኣንድ በኩል፤ ብኣዴንና ኦህዴድ በሌላ መስመር ተሰልፈው ሲወቃቀሱ ነበር።
ሊቀ መንበሩ ሃይለማርያም ደሳለኝ የቡዱናዊ መንገድ ከተመለከቱ በኋላ የኢህኣዴግ ስብሰባ ኣቁመው የድርጅቶቹ በግላቸው ገምግመው እንዲመለሱ በማለት መላው ቀይረው ጉብኝት ለማድረግ ብለው ወደ ምዕራብ ኣፍሪካ ሄደዋል።
በኢህኣዴግ ማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ለመሳተፍ የሞከሩት ኣቦይ ስብሓት ነጋና ኣቶ ኣባይ ፀሃየ “ስብሰባው ለኢህኣዴግ ማእከላዊ ኮሚቴ ኣባላት ብቻ የሚመለከት ስለሆነ ኣዳራሹ ለቃቹ ውጡልን” ተብለው በብኣዴን፣ ኦህዴድ ድርጅቶችና በነ ኣባይ ወልዱ የሚመራው ኣንጃ ተቃውሞ ስለ ደረሰባቸው በብስጭት ሳይወዱ በግድ ከስብሰባው ወጥተዋል።
ኣቦይ ስብሓት ነጋ በራሳቸው የደረሳቸው ጠንካራ ተቃውሞና ህወሓት በኢህኣዴግ የነበረው ተሰሚነት ማሽቆልቆሉ ኣስደንግጧቸዋል።
ለዚህ ጭንቀታቸው መፍትሄ ብለው የመረጡት መንገድ የመከላከያ ኢታማዦር ሹም ፕ/ጀነራል ሳሞራ ዮንስና የብሄራዊ ደህንነት ሃላፊ ኣቶ ጌታቸው ኣሰፋ በሽምግልና እየያዙዋቸው ይገኛሉ።

የኣቦይ ስብሓት ተማፅኖ “መንግስታችን የቆመው በ60 ሺ መስዋእትነት ነው እያልን የመጣነው ለፕሮፖጋንዳ እንዲመቸን ነው(ህዝቡን ዋሽተነዋል) እንጂ በትጥቅ ትግል የተሰዋው ከ200 ሺ በላይ ውድ የሰው ሂወት ነው” ካሉ በኋላ “ይህ ሁሉ መስዋእትነት የተከፈለበት ትግላችን እያየነው ወደ ጠላቶቻችን እጅ እየገባ ነው፣ ድርጅታችን ከዚ ውድቀት ለማውጣትና ስርዓታችን ከውድቀት ለማዳን ኣስፈላጊ እርምጃ ለመውሰድ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ኣለባቹ” የሚል ሓሳብና ተማፅኖ ኣቅርቦውላቸዋል።
በኣዲስ ኣበባ ለስብሰባ የተቀመጠው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ እየደረሰበት ያለው ተፅእኖ ለማብረድ በማሰብ “በትግራይ እየተካሄደ ያለው ልማት የሚቃወም ማንኛውም ሰው ከኣፍራሽ ተግባሩ እንዲቆጠብ…”የሚል መግለጫ ማውጣታቸው ይታወቃል።
የኣቦይ ስብሓት በትጥቅ ትግል ስለ ተከፈለው የሂወት መስዋእትነት ለ25 ዓመታት 60 ሺ ሲሉን ቆይተው ኣሁን ደርሰው 200 ሺ ነው የተከፈለው በማለት ስርዓቱ ለማቆየት ትልቅ ትኩረት እንዲሰጠው በመፈለግ ነው።
ስለ ኣጠቃላይ የድርጅቱ ንትርክ መረጃው ሲደርሰን እናካፍላቹሃለን።
ነፃነታችን በእጃችን ነው።

Wednesday, April 13, 2016

እስከ 25 ዓመታት እስራት የሚያስቀጣ የኮምፒዩተር ወንጀል አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ

የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ፡፡ በወታደራዊ ወይም ለዓለም አቀፍ ግንኙነት ሲባል በተሰየመ የኮምፒዩተር ዳታ ላይ የወንጀል ጥፋት የተሰነዘረ እንደሆነ፣ ድርጊቱ ከ15 እስከ 25 ዓመታት ጽኑ እስራት እንደሚያስቀጣ ይገልጻል፡፡

ይህ ቅጣት የሚጣለው ለወታደራዊና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሲባል ጥብቅ ሚስጥር በተባለ የኮምፒዩተር መረጃን (ዳታ) ያለፈቃድ ያገኘ፣ በሕገወጥ መንገድ የጠለፈ፣ እንዲሁም በኮምፒዩተር ሥርዓት ላይ ጣልቃ የገባ እንደሆነና ድርጊቱ የተፈጸመው በአገሪቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በታወጀበት ወይም አገሪቱ በአሥጊ ሁኔታ ላይ በምትገኝበት ወቅት ከሆነ ነው፡፡
ማክሰኞ ሚያዚያ 4 ቀን 2008 ዓ.ም. ለፓርላማው የቀረበው የዚህ ረቂቅ አዋጅ ማብራሪያ እንደሚያስረዳው፣ የኮምፒዩተር ወንጀል አዋጅን ማውጣት ያስፈለገው በአገሪቱ እየደረሱ ያሉ የኮምፒዩተር ወንጀሎች (የሳይበር ጥቃቶች) እና ተጋላጭነትን መሠረት በማድረግ ነው፡፡
የረቂቅ አዋጁ ክፍል ሁለት እንደሚያስረዳው ማንኛውም ሰው ሆነ ብሎ ያለፈቃድ ወይም ከተሰጠው ፈቃድ ውጪ ይፋዊ ያልሆነን የኮምፒዩተር ዳታ ወይም የዳታ ፕሮሰሲንግ አገልግሎት የጠለፈ እንደሆነ፣ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራትና ከ10,000 እስከ 50,000 ብር በሚደርስ መቀጮ ይጣልበታል፡፡
ጠለፋው የተካሄደው በቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ ማለትም በወታደራዊ የዕዝ ቁጥጥር ሲስተሞች፣ የደኅንነት፣ የፍትሕና የፀጥታ ተቋማት ሚስጥራዊ ዳታዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የትራንስፖርት የኮምፒዩተር ሲስተሞች፣ መሠረታዊ የሕዝብ አገልግሎቶችና የመሳሰሉት ላይ ከሆነ ከ10 ዓመት እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራትና ከ50,000 እስከ 100,000 ብር እንደሚያስቀጣ ይገልጻል፡፡
ረቂቅ አዋጁ ጠለፋ ማለት በኮሙዩኒኬሽን ሒደት ላይ ያለን የኮምፒዩተር ዳታ ወይም የዳታ ፕሮሰሲንግ አገልግሎት መከታተል፣ መቅዳት፣ ማዳመጥ፣ መውሰድ፣ ማየት፣ መቆጣጠር ወይም ሌላ ተመሳሳይ ድርጊት መሆኑን ያስረዳል፡፡
በሰዎች የነፃነትና ክብር ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች በሚል ንዑስ ርዕስ በአንቀጽ 13 ላይ የኮምፒዩተር ሥርዓትን በመጠቀም በሚሠራጭ ጽሑፍ፣ ንግግር፣ ቪዲዮ ወይም ሥዕል አማካይነት በሌላ ሰው ወይም በተጐጂው ቤተሰቦች ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ ያስፈራራ ወይም የዛተ ከሦስት እስከ አምስት ዓመት ጽኑ እስራት ያስቀጣል፡፡
በሕዝብ ደኅንነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች በሚለው በረቂቁ አንቀጽ 14 ላይ፣ ‹‹ማንኛውም ሰው በኅብረተሰቡ መካከል የፍርኃት ስሜት፣ አመፅ፣ ሁከት፣ ወይም ግጭት እንዲፈጠር የሚያነሳሳ ጽሑፍ፣ ተንቀሳቃሽ ምሥል፣ ድምፅ ወይም ማንኛውም ሌላ ምሥል በኮምፒዩተር ሥርዓት አማካይነት ያሠራጨ እንደሆነ ከሦስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ያስቀጣል፤›› ይላል፡፡
የ‹ስፓም› መልዕክቶችን ስለማሠራጨት በሚለው የረቂቁ አንቀጽ 15 ድንጋጌ መሠረት ማንኛውም ሰው ምርትን ወይም አገልግሎትን ለማስተዋወቅ ወይም ለሽያጭ ለማቅረብ፣ መልዕክቶችን በአንድ ጊዜ ወደ በርካታ ኢሜል አድራሻዎች ያሠራጨ እንደሆነ ከሦስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት መቀጮ ያስቀጣል፡፡ ወንጀሉ ከባድ በሆነ ጊዜ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራትና ከ50,000 ብር በማይበልጥ መቀጮ ያስቀጣል፡፡ ረቂቁን የተመለከተው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለዝርዝር ዕይታ ለሕግና ፍትሕ አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል፡፡  
ሰሞኑን የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ለፓርላማ ያቀረቡት የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል ከውጭ አገሮች በተሰነዘረ የኮምፒዩተር ጥቃት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው የፌዴራል መንግሥት የዳታ ማዕከል አካል የሆነው የወረዳ ኔት ላይ ጥቃት መሰንዘሩን መናገራቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
ይህንንም ጥቃት ዶ/ር ደብረ ጽዮን በኦሮሚያ ከተቀሰቀሰው አመፅ ጋር በማገናኘት ለማቀጣጠል ያቀዱ የሰነዘሩት መሆኑን፣ ነገር ግን በመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲና በሌሎች ባለድርሻ አካላት በቁጥጥር ሥር መዋሉን መናገራቸውንም መዘገባችን አይዘነጋም፡፡

Tuesday, March 15, 2016

ቃለ መጠየቅ ከጋዜጠኛና መምህርት ሪዮት ዓለሙ ጋር 05-02-2016

ከጥያቄዎች መካከል ጥቂቶቹ

ጋዜጠኛነዎት ወይንስ የዲሞክራሲ ታጋይ?
ብርቱካን መዴክሳ ሞዴልዎት ናቸው?
ለዲሞክራሲ ግንባታ ለሚደረገው ጥረት ከሴቶች ምን ይጠበቃል?
አረቡ አብዮት ስኬተማ የሆነችው አገር ቱኒዚያ ናት
ለስኬት ያበቃት ደግሞ የሰላም ኖብል ሽልማት ተሻላሚ የሆነው
አወያይ ቡድን ነው ኢትዮጵያ ከቱኒዚያ ምን ትማራለች?


የሚሉት ይገኙበታል